NEME - your only gateway to info. on Islam in Ethiopia and Ethiopian Muslims

O mankind! We created you from male and female, and made you into nations and tribes, so that you may come to know one another. Truly, the most honoured of you in God's sight is the greatest of you in piety. God is All-Knowing, All-Aware. (Qur'an, 49:13)

 
 
 
 Event:- Online Lecture - at 21:00 cet.
WWW NEME
Bilal ul-Habasha
Ethiopian Muslims Community Platform
NOTE: You need to have Unicode Geez font installed on your PC to read the article below. Please click for a PDF version of the text.

ሚያዚያ 23, 1998

ለእስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ጽ/ቤት
አዲስ አበባ
ኢትዮጵያ

ትክክለኛው ምክንያት ግልፅ ያልሆነው በቅርቡ በአገራችን ቅዱስ ቁርዓኑን ባልሆነና ባልተገባ ቦታ በአፀያፊ መልኩ በመጠቀም የተከሰተው ድርጊት አሳዛኝና አሳፋሪ ከመሆኑም በላይ ፍትሃዊ መልስ ሊሰጥበት የሚገባ አጣዳፊ ጉዳይ ነው

በወሎ ከሚሴ እንደዚሁም በኢትዮጵያ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በአዋሳ ደቡብ ዩኒቨርሲቲበአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲና ቀጥሎም በጅማ ዩኒቨርሲቲ የደረሰዉ የቁርዓንንና የነቢዩ ሙሐመድን (የአላህ ሰላምና በረከት በእርሳቸው ላይ ይዉረድ) ማንነት ለማራከስ የተደረገዉ ሙከራ ከአፀያፊና አሳፋሪነት ባሻገር ድርጊቱ ከሰፊው የኢትዮጵዊያ ሕዝብ የረጅም ጊዜ አብሮ የመኖርና የመቻቻል ሕይወት ታሪክ ጋር አብሮ የማይሄድ ነው

ምንም እንኳን ድርጊቱ የጥቂት ተንኮለኞች ጉዳይ መሆኑን መገመት ቢቻልም እነዚህ ተንኮለኞች አገር አጥፊ ድርጊታቸውም ሆነ ምኞታቸው ሥር እንዳይሰድ በአፋጣኝ ለፍርድ ቀርበው ተገቢ እርምጃ ሊወሰድባቸው ይገባልየተደረገው ድርጊት የኢትዮጵዊያን ሙስሊሞችን ስነ-ልቦና የሚጎዳ ብቻ ሳይሆን በመላው ዓለም የሚኖሩትን ከ1.5 ቢሊዮን በላይ የሚቆጠሩ ሙስሊሞችን ሰሜት የሚነካ መሆኑ ጉዳዮን አሳሳቢ ያደርገዋል

ኢትዮጵያ ሀገራችን በቀያቸው የእምነት ነፃነትን በመነፈጋቸው የእምነትን ከለላ የፈለጉ የሙስሊም ስደተኞችን ተቀብላ ያስተናገደች የመጀመሪያዋ የስደት/የሂጅራ አገር (the land of First Hijra)፤ በጊዜው ከመካ ቀጥሎ እስልምና የተሰበከባት በዓለም የመጀመሪያዋ ሀገር ነችታድያ ይህ አኩሪ ታሪካችን በማንኛውም ኢትዮጵያዊ ዘንድ መዘንጋት ይቅርና ችላ ሊባልም የሚገባዉ ነገር አይደለምከዚህም አንፃር አሁን የደረሰው ሁኔታ ለዚህ ተቻችሎ ለኖረ ሕዝብ ሊያሳስበዉሊያስጨንቀውና ሊያስቆጨው ይገባል

የተወሰኑ ክፍሎች ይኽን ሀቅ ከተጨባጩ የሕዝብ አብሮ የመኖር ፍቅር በመነጠል ለዕኩይ ዓላማቸው መተግበሪያ ሊያውሉት መሞከር ፋይዳ የማይኖረው ከንቱ ልፋት መሆኑን ከታሪክ ሊማሩ ይገባቸዋልእኛ ኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞችና ክርስቲያኖች ቁርዓን አህሉል-ኪታብ ብሎ የሚጠራን የመጽሐፍ ሰዎች ቤተሰብ ነን

ሀገራችን ኢትዮጵያ ዛሬ ካለችበት ዉስብስብ ችግርና የድህነት ቀንበር ልትወጣ የምትችለው በሕዝቦቿ መካከል በመከባበርና በመግባባት ላይ የተመሰረተ ሰላም ሲኖር ብቻ ነውለዚህም እገሌ ከእገሌ ሣንል የባህላችን አንድ ገጽታ የሆነዉን መከባበርና መቻቻል ምርኩዝ አድርገን ጠንክረን መያዝና ለገቢራዊነቱም በርትተን መስራት ይጠበቅብናል

በዚህ አጋጣሚ ለመላው ኢትዮጵያዊን ሙስሊም ወገኖቼ የተሰማኝን ጥልቅ ሀዘን እገልጻለሁይህ አሳፋሪ ጉዳይም በአስቸኳይ በሚመለከተው ክፍል ተጣርቶ ጥፋተኞች ለፍርድ እንዲቀርቡአስፈላጊና የማያዳግምም ቅጣት እንዲሰጣቸው እጠይቃለሁ

ሰላም ለኢትዮጵያ ሕዝብ!

ከዶ/ር ልጅ አስፋ-ወሰን አስራተ-ካሳ
ፍራንክፈርት
ጀርመን

Online - Activity
20/01/06
Lecture
Dawa & Da'iyah
(Sh. Adem Kamil)
23/12/05
Lect. + Q&A
(Sh. Adem Kamil)
Radio Negashi (Stockholm, Sweden)
Radio First Hijra
(Washington DC.)
Week of

Latest
U P L O A D

O N L I N E
L e c t u r e s

Next Lecture'll be on at kemishitu 4:00 se'at (Ethio)/ 21:00 cet/ 10:00 pm Mekka, Insha Allah. Learn more

- More Audio
- Ask the Scholar


Subscribe to the NEME egroup


Your are visitor

since 28/02/2004!

Network of Ethiopian Muslims in Europe, NEME © 2004-2005 All Right Reserved.
NEME has no the policy of editing or rejecting to publish the views of any participant, unless it incites hatred and the like, be it against individuals or groups. In that case, NEME deserves the right to deny space for such opinions in its site. NEME would like to remind all those who wish to make use of our service thus that we stand for understanding, respect and unity of the Muslim umma, and not for hatred, division, or sectorianism of any sort - all these are abhorred by the Amighty Allah (sw) and His final and beloved Prophet (saw). NEME promotes tolerance and peaceful co-existence of Ethiopians of all faith.

Views and opinions expressed in the articles we publish are that of the contributer(s) and do not necessarily reflect the position of NEME.