በሃገራችን
በቅዱስ
ቁርዓን ላይ
የተፈፀመውን
ፀረ ኢስላም
ወንጀል አስመልክቶ
ከነጃሺ የኢትዮጵያውያን
ሙስሊሞች
ማህበር በስዊድን
የተሰጠ መግለጫ
ቢስሚላሂ
አረህማን አረሁም
በሃገራችን
ታላላቅ የከፍተኛ
ትምህርት ተቋማት ውስጥ
ቅዱስ ቁርዓንን
ለሽንት ቤት
መፀዳጃነት በመጠቀም
የተፈፀመውን እጅግ
በጣም አሳፋሪ የሆነ
ፀረ ኢስላም ወንጀል የሰማነው
ጥልቅ በሆነ ሃዘንና
ምሬት ነው።
በሙስሊሞች
ዘንድ ቅዱስ ቁርዓን
ያለው ቦታ ከምንም
ነገር በላይ ከፍ ያለ
ነው። ቅዱስ ቁርዓን
የሰው ልጆች ቀጥተኛ
ወደሆነው ጎዳና ይመሩ
ዘንድ ከፈጣሪያችን
አላህ ለነብዮ መሃመድ
የተገለጸ የምህረት
ቃል ነው። በዚህም
የተነሳ ሙስሊሙች የሰውነታቸውን
የተለያዩ ክፍሎች
በውሃ ካላጠሩ ወይንም
ውዱዕ ካላደረጉ በስተቀር
አይነኩትም። ለዚህም
ነው ቅዱስ ቁርዓን
ላይ የተፈፀመው ወንጀል
በሙስሊሙች ዘንድ
ለአስከፊነቱ ወደር
የማይገኝለት። ኢትዮጵያ ሙስሊሞችና
የሌሎች እምነት
ተከታዮች ጎን ለጎን
በመሆን ለረጂም
ዘመናት የኖሩባት
ሃገር ናት።
በእስልምናና
ክርስትና እምነት
ተከታዮች መካከል
የነበሩት ግንኙነቶች
ሁልጊዜ በእኩልነትና
በመቻቻል ላይ
የተመሰረቱ ነበሩ ብሎ
ለመናገር አይቻልም።
ለዚህም በርካታ
የታሪክ መረጃዎችን
መጥቀስ ይቻላል።
ከአፄዎቹ ስርአት
መደምሰስ ወዲህ ግን
ሁኔታዎች የመሻሻል
አዝማሚያ አሳይተውል
ማለት ስህተት አይሆንም።
ያም ሆኖ ግን በተለይ
በአሁኑ አለማችን ላይ
በሃይማኖቶች ግጭት
ሳቢያ ብዙ ደም
በሚፈስበት ወቅት
እንዲህ ያለው
የሃገሪቱ ግማሽ አካል
የሁነውን የሙስሊሙን
ልብ ክፉኛ ያቆሰለና
ሌሎች ሠላም ወዳድ
ዜጎችን ያሳዘነ ፀረ
ኢስላም ወንጀል
መፈፀሙ ሃገሪቱን ወደ
ከፋ ችግር ውስጥ
ሊጨምራት እንደሚችል
መገመት አዳጋች
አይሆንም።
ነጃሺ
የኢትዮጵያውያን
ሙስሊሞች ማህበር
በስዊደን
የተቋቋመበት አላማ
በስዊደን የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን
ሙስሊሞች
የሃይማኖታቸውንና
የባህሎቻቸውን
እሴቶች ሳይለቁ
ከቀሪው ህብረተሰብ
ጋር በጋራ
የሚኖሩበትን ሁኔታ
ለማመቻቸት ነው።
ለሃገራችን ኢትዮጵያ
ሠላም ፣ እድገትና
ብልጽግናም እንዲሁ
የበኩላቸውን
አወንታዊ አስተዋፅዖ
የሚያደርጉበትን
መንገድ ይከፍታል።
ከዚህ መንፈስ
በመነሳት በቅዱስ
ቁርዓናችን ላይ
በተሰነዘረው አፀያፊ
ፀረ ኢስላም ወንጀል
ሣቢያ ሃገራችን ላይ
ያጠለለው የጥፋት
ደመና ይገፈፍ ዘንድ
ፍላጎታችንም
የምንታገልለትም
አላማ ነው። ይህም
ትግላችን ይሰምር
ዘንድ ከዚህ በታች
የተዘረዘሩ
ጥያቄዎቻችንን ምላሽ
እንዲያገኙ የኢትዮጵያን
መንግስት
እንጠይቃለን።
1.
ለወንጀሉ
ተጠያቂ የሆኑት
ግለሰቦች ለፍርድ
ቀርበው ለጥፋታቸው
ተመጣጣኝ የሆነ
ቅጣትን እንዲቀበሉ
2.
ወንጀሉን
ከፈፀሙት ግለሰቦች
ጀርባ ሊኖር የሚችለው
የተቀነባበረ ሴራ እንዲመረመርና
ግልጽ እንዲደረግ
3.
ተመሳሳይ
ወንጀሎች በድጋሚ
እንዳይፈጸሙ
አስፈላጊ እርምጃዎች
እንዲወሰዱ።
ይህ
በሃገራችን ብሄራዊ
ደህንነት ላይና
በተለይ ደግሞ
በሙስሊሞች ላይ የተሰነዘረው
አፀያፊ ፀረ ኢስላም
ወንጀል ከፍተኛ
እንደመሆኑ መጠን የሚያስከትለውም
መዘዝ የዚያኑ ያህል
ከፍተኛና ዘላቂ ሊሆን
የሚችል ነው።
ይህንንም ከግምት
ውስጥ በማስገባት
መንግስት ለጉዳዩ
ከፍተኛ ትኩረትን
በመስጠት
ፀረ ኢስላም ወንጀል
በሃገሪቱ ህገ
መንግስትም ሆነ
በስልጣን ላይ ባለው
ፓርቲ ተቀባይነት
የሌለው መሆኑን
በማሳየት በወንጀሉ
ሳቢያ ሊከተሉ የሚችሉ
የአጭርና የረጅም ጊዜ
መዘዞችን
እንዲከላከል
እናሳስባለን።
በፍትህና
በመብት እኩልነት
ላይ የተመሰረተች
የበለፀገች
ሰላማዊት
ኢትዮጵያን
ለመመሥረት
ባንድነት እንነሳ!
የነጃሺ
የኢትዮጵያውያን
ሙስሊሞች ማህበር
በስዊድን
የሥራ
አስኪያጅ ኮሚቴ