Ramadhan Reminder, 17.09.1427

In the Name of Allah, the Merciful, the Compassionate


In the Name of Allah, the Merciful, the Compassionate

Q021:092-094
Verily, this brotherhood of yours is a single brotherhood, and I am your Lord and Cherisher: therefore serve Me (and no other). But (later generations) cut off their affair (of unity), one from another: (yet) will they all return to Us.

Whoever works any act of righteousness and has faith,- His endeavour will not be rejected: We shall record it in his favour.

Q022:011-012
And among men is he who serves Allah (standing) on the verge, so that if good befalls him he is satisfied therewith, but if a trial afflict him he turns back headlong; he loses this world as well as the hereafter; that is a manifest loss.

He calls besides Allah upon that which does not harm him and that which does not profit him, that is the great straying.

Q022:017
Surely those who believe and those who are Jews and the Sabeans and the Christians and the Magians and those who associate (others with Allah)-- surely Allah will decide between them on the day of resurrection; surely Allah is a witness over all things.

Q022:077-078
O you who believe! bow down and prostrate yourselves and serve your Lord, and do good that you may succeed.

And strive hard in (the way of) Allah, (such) a striving as is due to Him; He has chosen you and has not laid upon you an hardship in religion; the faith of your father Ibrahim; He named you Muslims before and in this, that the Messenger may be a bearer of witness to you, and you may be bearers of witness to the people; therefore keep up prayer and pay the poor-rate and hold fast by Allah; He is your Guardian; how excellent the Guardian and how excellent the Helper!

በአላህ ስም እጅግ በጣም ርኅሩኅ በጣም አዛኝ በኾነው

ቁ.021፡092-094
ይህች (ሕግጋት) አንዲት መንገድ ስትኾን በእርግጥ ሃይማኖታችሁ ናት፤ እኔም ጌታችሁ ነኝና ተገዙኝ። በሃይማኖታቸዉም ነገር በመካከላቸው ተለያዩ፤ ሁሉም ወደኛ ተመላሾች ናቸው።

እርሱ ያመነ ኾኖ ከበጎ ሥራዎች ማንኝዉንም የሚሠራም ሰው ምንዳውን አይነፈግም፤ እኛም ለርሱ መዝጋቢዎች ነን።

ቁ.022፡011-012
ከሰዎችም (ከሃይማኖት) በጫፍ ላይ ኾኖ አላህን የሚግገዛ ሰው አለ፤ ታዲያ መልካም ነገር ቢያገኘው በርሱ ይረጋል፤ መከራም ብታገኘው በፊቱ ላይ ይገለበጣል፤ የቅርቢቱን ዓለምም የመጨረሻይቱንም ከሰረ፤ ይህ እርሱ ግልጽ ከሳራ ነው። ከአላህ ሌላ የማይጎዳዉና የማይጠቅመዉን ይግገዛል፤ ይህ እርሱ (ከእዉነት) የራቀ ስሕተት ነው።

ቁ.022፡017
እነዚያ ያምኑ፣ እነዚያም ይሁዳዊያን የኾኑ፣ ሳቢያኖችም፣ ክርስቲያኖችም፣ መጂሶችም (በፀሀይና በጨረቃ በእሳት የሚያመልኩ) እነዚያም (ጣዖታትን በአላህ) ያጋሩ፤ አላህ በትንሳኤ ቀን በመካከላቸው በፍርድ ይለያል፤ አላህ በነገሩ ሁሉ ላይ በእርግጥ አዋቂ ነውና።

ቁ.022፡077-078
እናንተ ያመናችሁ ሰዎች ሆይ! (በስግደታችሁ) አጎንብሱ፣ ብግንባራችሁም ተደፉ፤ ጌታችሁንም ተገዙ፤ በጎንም ነገር ሥሩ፤ ልትድኑ ይከጀልላችኋልና።

በአላህም ሃይማኖት ተገቢዉን ትግል ታገሉ፤ እርሱ መርጧችኋል፤ በናንትም ላይ በሃይማኖቱ ዉስጥ ምንም ችግር አላደረገባችሁም፤ የአባታችሁን የኢብራሂምን ሃይማኖት ትከተሉ፤ እርሱ ከዚህ በፊት ሙስሊሞች ብሎ ሰይሟችኋል፤ በዚህም (ቁርአን)፤ መልክተኛዉ በናንተ ላይ መስካሪ እንዲኾን እናንተም በሰዎቹ ላይ መስካሪዎች እንድትኾኑ (ሙስሊሞች ብሎ ሰይሟችኋል)፤ ሰላትንም አስተካክላችሁ ስገዱ፣ ዘካንም ስጡ፤ በአላህም ተጠበቁ፤ እርሱ ረዳታችሁ ነው፤ (እርሱ) ምን ይምር ጠባቂ! ምን ያምር ረዳት!

O my Lord! Expand my breast for me, And make my affair easy to me, And remove the impediment from my speech, So they may understand what I say. (Q020:025-028) Our Lord! grant us mercy from Thee, and provide for us a right course in our affair.(Q18:010) My Lord! make me to enter a goodly entering, and cause me to go forth a goodly going forth, and grant me from near Thee power to assist (me). (Q17:080)